Author - ABA

የጨረታ ማስታዎቂያ

ፀደይ ባንክ (አ.ማ) ለአቶ ጌታቸው አባት ለሰጠው ብድር በዋስትና የያዛቸውን በሰንጠረዡ የተዘረዘሩ መኖሪያ ቤቶችን በአዋጅ ቁጥር 97/90 በተሸሻለው አዋጅ ቁጥር 216/92 በተሰጠው ስልጣን መሰረት በግልጽ ጨረታ አወዳድሮ ለመሸጥ ይፈልጋል፡፡ በመሆኑም ተጫራጮች ለጨረታ ከመቅረባቸው በፊት የሚከተሉትን ደንቦች መገንዘብ ይኖርባቸዋል፡፡ ተጫራጮች የቤቱን የጨረታ መነሻ ዋጋ ¼ (በጥሬ ገንዘብ ወይም ሲ.ፒ.ኦ በፀደይ ባንክ ስም (አ.ማ) በማሰራት ለጨረታ ማስከበሪያ በማስያዝ በጨረታው መሳተፍ ይችላሉ፡፡ በጨረታው የሚሳተፈው በሕግ ሰውነት ያገኘ ሰው ከሆነ የድርጅቱ መመሥረቻ ጽሑፍ ወይም መተዳደሪያ ደንብ፣ ሕጋዊ ሰውነት ያገኘበት የምዝገባ የምስክር ወረቀት እንዲሁም ሕጋዊ ውክልና ማቅረብ...

ፀደይ ባንክ ከኢትዮጵያ ምርት ገበያ ባለስልጣን ጋር የክፍያ አጋርነት የመግባቢያ ሰነድ ተፈራረመ፡፡

ፀደይ ባንክ ከኢትዮጵያ ምርት ገበያ ባለስልጣን ጋር አብሮ ለመስራት የሚያስችለውን የመግባቢያ ሰነድ ዛሬ ጥቅምት 8/2017 ዓ.ም ተፈራርሟል፡፡ ስምምነቱ ፀደይ ባንክ የኢትዮጵያ ምርት ገበያ ባለስልጣን የሚሰጠውን የክፍያ እና የርክክብ ስርዓት ለማቀላጠፍ እንዲሁም በመጋዝን ደረሰኝ ብድር ተጠቃሚነት አገልግሎት ለመስጠት የሚያስችል ነው፡፡ የስምምነቱን ፋይዳ በተመለከተ የፀደይ ባንክ ፕሬዚዳንት አቶ መኮንን የለውምወሰን እና የኢትዮጵያ ምርት ገበያ ባለሥልጣን ዋና ሥራ አስፈፃሚ አቶ ወንድምአገኝ ነገራ በጋራ መግለጫ ሰጥተዋል፡፡ የፀደይ ባንክ ፕሬዚዳንት አቶ መኮንን የለውምወሰን ባለሥልጣኑ አገልግሎቱን እያቀረበላቸው ያሉት አርሦ አደሮች እና አምራች የማኅበረሰብ ክፍሎች ወደ ምርት ገበያው መጥተው ምርታቸውን...

የፀደይ ባንክ አ.ማ የባለአክሲዮኖች 4ኛ መደበኛ ጠቅላላ ጉባኤ ጥሪ

ለተከበራችሁ የፀደይ ባንክ አ.ማ ባለአክሲዮኖች፤ የፀደይ ባንክ አ.ማ የባለአክሲዮኖች 4ኛው መደበኛ ጠቅላላ ጉባዔ (የተደገመ) በኢትዮጵያ ንግድ ህግ ቁጥር 1243/2013 አንቀጽ 366፤ 367፤ 370፤371 እና 372 መሠረት ቅዳሜ ጥቅምት 30 ቀን 2017 ዓ.ም ከጠዋቱ 2፡30 ሰዓት ጀምሮ ሸራተን ሆቴል ይካሄዳል፡፡ ስለሆነም የባንኩ ባለአክሲዮኖች በአካል ወይም በህጋዊ ወኪሎቻችሁ አማካኝነት በተጠቀሰው ቀን: ሰዓት እና ቦታ እንድትገኙ የዳይሬክተሮች ቦርድ ጥሪውን በአክብሮት ያቀርባል፡፡ ስለባንኩ መግለጫ:- የባንኩ የተፈረመ ካፒታል፡                                    ብር 9,837,889,000.00 የባንኩ የተከፈለ ካፒታል፡                                      ብር 9,833,346,171.87 የባንኩ ዋና የንግድ ምዝገባ ቁጥር ፡                            MT/AA/3/0052707/2014 የባንኩ የሥራ ፈቃድ ቁጥር:                                    LBB/TM/026/2022 የባንኩ አድራሻ፡ አዲስ አበባ ከተማ፣ቂርቆስ...

ለውድ የፀደይ ባንክ ደንበኞች!

መንግሥት በቅርቡ ባወጣው የተጨማሪ እሴት ታክስ አዋጅ ቁጥር 1341/2016 መሠረት የፋይናንስ ተቋማት በሚሰጧቸው አገልግሎቶች ላይ ተጨማሪ እሴት ታክስ እንዲሰበስቡ ተመላክቷል፡፡ ባንካችን ፀደይም ይህንን ኀላፊነት ለመወጣት ከመስከረም 21/2017 ዓ.ም ጀምሮ በባንኩ አገልግሎቶች ላይ ተጨማሪ እሴት ታክስ የሚያስከፍል መሆኑን ለውድ ደንበኞቹ በአክብሮት ያሳውቃል፡፡ ፀደይ ባንክየሁሉም ባንክ!

ፀደይ ባንክ ድጋፍ ለሚሹ ሕጻናት ግማሽ ሚሊዮን ብር በሚጠጋ ወጪ የትምሕርት ቁሳቁስ ድጋፍ አደረገ፡፡

ፀደይ ባንክ ግማሽ ሚሊዮን ብር በሚጠጋ ወጪ ድጋፍ ለሚሹ 500 ተማሪዎች 500 ደርዘን ደብተር እና 50 ፓኬት እስክርቢቶ ድጋፍ አድርጓል። ሰውን በሚያስቀድሙ ማኅበራዊ ኀላፊነቶች የሚታወቀው የሁሉም የሆነው ፀደይ ባንክ በበርካታ ዘርፎች ማኅበራዊ ኀላፊነቱን እየተወጣ ይገኛል፡፡ ባንኩ 500, 000 ብር የሚጠጋ ገንዘብ ወጪ በማድረግም ከዝግባ የሕፃናት እና የአረጋዊያን በጎ አድራጎት ድርጅት ጋር በመተባበር ድጋፍ ለሚሹ ተማሪዎች 500 ደርዘን ደብተር እና 50 ፓኬት እስክርቢቶ ድጋፍ አድርጓል፡፡ በድጋፍ መርሐ-ግብሩ ላይ የተገኙት የፀደይ ባንክ ኮርፖሬት ማርኬቲንግ እና ኮሚዩኒኬሽን ዳይሬክተር ቢራራ በዜ (ዶክተር) ባንኩ የሁሉም ባንክ መሆኑን በተግባር...

ፀደይ ባንክ በስካይ ላይት ሆቴል የሐዋላ አውደ ርዕይ እየተሳተፈ፤ የሐዋላ ፕሮዳክቶቹንም እያስተዋዎቀ ነው፡፡

ፀደይ ባንክ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ ባዘጋጀው “ደቦ” የተሰኘ የሐዋላ ፍሰት ግንዛቤ ማስጨበጫ አውደ ርዕይ ላይ እየተሳተፈ ይገኛል:: በአውደ ርዕዩ ባንኩ "ታታሪዎቹ" የተሰኘውን የሐዋላ የቁጠባ አማራጭ እና ሌሎችንም ፕሮዳክት እና አገልግሎቶች እያስተዋወቀ ይገኛል፡፡ ታታሪዎቹ የቁጠባ ሒሳብ •  የውጭ ሀገራት ገንዘብ ወደ ሀገር ቤት ለሚልኩ ታታሪዎች በቀላሉ ተደራሽ የሆነ  የቁጠባ አማራጭ •  ከራሳቸው አልፎ ለቤተሰባቸው ኑሮ መሻሻል ለሚተጉ በውጭ ሀገራት ለሚኖሩ ሁሉም ታታሪዎች የተዘጋጀ •  ወለድ የሚያስገኙ እና የማያስገኙ የቁጠባ አማራጮች ያሉት •  ዝቅተኛ የቅድመ ክፍያ እና ምቹ የብድር አከፋፈል አማራጮች የሚመቻችበት •  ከሐዋላ ጋር ለተያያዙ የገንዘብ ዝውውሮች ልዩ...

የጨረታ ማስታዎቂያ

ፀደይ ባንክ (አ.ማ) ለአቶ ጌታቸው አባት ለሰጠው ብድር በዋስትና የያዛቸውን በሰንጠረጁየተዘረዘሩ መኖሪያ ቤቶችን በአዋጅ ቁጥር 97/90 በተሸሻለው አዋጅ ቁጥር 216/92 በተሰጠውስልጣን መሰረት በግልጽ ጨረታ አወዳድሮ ለመሸጥ ይፈልጋል፡፡ በመሆኑም ተጫራጮች ለጨረታ ከመቅረባቸው በፊት የሚከተሉትን ደንቦች መገንዘብ ይኖርባቸዋል፡፡ ተጫራጮች የቤቱን የጨረታ መነሻ ዋጋ ¼(በባንክ በተረጋገጠ ቼክ ወይም ሲ.ፒ.ኦበፀደይ ባንክ ስም (አ.ማ) በማሰራት ለጨረታ ማስከበሪያ በማሲያዝ በጨረታው መሳተፍይችላሉ፡፡ ለጨረታው የሚሳተፈው በህግ ሰውነት ያገኘ ሰው ከሆነ የድርጅቱ መመስረቻ ጹሁፍወይም መተዳደሪያ ደንብ ፣ህጋዊ ሰውነት ያገኘበት የምዝገባ የምስክር ወረቀትእንዲሁም ህጋዊ ውክልና ማቅረብ አለበት፡፡ የጨረታው አሸናፊ አሸናፊነቱ የሚረጋገጠው የጨረታው ውጤት...

ፀደይ ባንክ እና የፌዴራል ሰነዶች ማረጋገጫ እና ምዝገባ አገልግሎት በጋራ ለመሥራት ተፈራረሙ፡፡

ፀደይ ባንክ እና የፌዴራል ሰነዶች ማረጋገጫ እና ምዝገባ ኤጀንሲ በጋራ ለመሥራት ዛሬ ሐምሌ 09/2016 ዓ.ም በባንኩ ዋና መሥሪያ ቤት ተፈራርመዋል፡፡ በፀደይ ባንክ በኩል ስምምነቱን የፈረሙት የዲጂታል እና ብራንች ባንኪንግ ምክትል ፕሬዚዳንት አቶ ቴዎድሮስ ታደሠ፣ ባንኩ ከ14 ሚሊዮን በላይ ደንበኞች እና ከ620 በላይ ቅርንጫፎች ያሉትና በመላ ሃገሪቱ ሰፊ ተደራሽነት ያለው መኾኑን ገልፀዋል፡፡ ስምምነቱም በውክልና የሚተዳደሩ የሰነድ መረጃዎችን ባንኩ ፈጣን እና ተደራሽ በኾነ መልኩ በቀላሉ ለማግኘት እንደሚያስችለው ገልፀዋል፡፡ የባንኩን አገልግሎት በማዘመን እና የደንበኞችን እርካታ በመጨመር በኩል ትልቅ ፋይዳ እንደሚኖረውም ተናግረዋል፡፡ የፌዴራል ሰነዶች ማረጋገጫ እና ምዝገባ...

ፀደይ ባንክ የ2023/24 አፈፃፀም እና 2024/25 እቅድ ላይ ውይይት አካሂዷል፡፡

የፀደይ ባንክ የ2023/24 አፈፃፀም እና 2024/25 እቅድ ላይ ውይይት ባንኩ የማኔጅመንት አባላት፣ የዲስትሪክት እና ዲቪዥን ሥራ አስኪያጆች በተገኙበት ነው የአፈፃፀም እና የእቅድ ውይይቱን ዛሬ ሐምሌ 22/2016 ዓ.ም በዋና መሥሪያ ቤቱ ያካሄደው። በውይይቱም የ2023/24 አፈፃፀሙን በጥልቀት በመገምገም የቀጣይ አቅጣጫዎችን አስቀምጧል። የ2024/25 እቅድ ላይም በስፋት ውይይት በማካሄድ የተሻለ አፈፃፀም ለማስመዝገብ መግባባት ላይ ተደርሷል። የፀደይ ባንክ የ2023/24 አፈፃፀም እና 2024/25 እቅድ ላይ ውይይት

የፀደይ ባንኩ አትሌት ዳዊት ቢተው በ1500 ሜትር ውድድር የፍፃሜ ውድድሩን በ1ኛነት አጠናቀቀ።

የኢትዮጵያ ወጣቶች አትሌቲክስ ሻምፒዮና በሲዳማ ክልላዊ መንግስት ከሰኔ 25/2016 እስከ ሰኔ 29/2016 ዓ.ም በሀዋሳ ከተማ እየተካሄደ ይገኛል። የፀደይ ባንክ አትሌቲክስ ክለብም በውድድሩ በተወሰኑ አትሌቶች አማካኝነት እየተወዳደረ ይገኛል። በዚህ ውድድር የፀደይ ባንኩ አትሌት ዳዊት ቢተው በ1500 ሜትር 1ኛ በመሆን የወርቅ ሜዳልያ አስገኝቷል። በውድድሩ በበላይነት ያጠናቀቀው አትሌት ዳዊት የክለቡ ባለቤት የሆነው ፀደይ ባንክ በሀዋሳ ኢንተርናሽናል ስታዲየም በተደጋጋሚ እንዲተዋዎቅ ማስቻሉን የክለቡ ሥራ አስኪያጅ ደሳለው እንዳለው ያደረሰን መረጃ ያመላክታል። በሌላ ዜና የፀደይ ባንክ አትሌት መቅደስ ሽመልስ የመቻል (የመከላከያ) ስፖርት አዲስ አበባ ከተማ ላይ ከሰሞኑ ባዘጋጀው የ10 ኪሎ...