ፀደይ ባንክ ቅርንጫፎቹን በሁሉም የሀገሪቱ ክፍሎች እያስፋፋ ነው፡፡
ፀደይ ባንክ የባንክ አገልግሎት መስጠት ከጀመረ ወዲህ ተጨማሪ 142 ቅርንጫፎችን መክፈቱን የባንኩ የዲጂታልና ብራንች ባንኪንግ ም/ፕሬዚዳንት አቶ ቴዎድሮስ ታደሰ ተናግረዋል፡፡ ይህ ዘገባ እስከተጠናቀረበት ጊዜ ድረስም የባንኩን ቅርንጫፎች ብዛት 608 ማድረስ ተችሏል፡፡ በደቡብ የሀገሪቱ ክፍል አርባ ምንጭ፣ ወላይታ ሶዶ፣ ዲላ፣ ሆሳዕና፣ ይርጋ ጨፌ፣ ሻሸመኔ እና ሀዋሳ ከተሞች ላይ ቅርንጫፎች ተከፍተው አገልግሎት እየሰጡ መሆኑን ያስረዱት አቶ ቴዎድሮስ በምስራቁ የሀገሪቱ ክፍል ደግሞ ድሬዳዋ፣ ሎጊያና አሳይታ ከተሞች ቅርንጫፎች መከፈታቸውን ገልጸዋል፡፡ በደቡብ ምዕራቡ የሀገሪቱ ክፍል ደግሞ ጅማ፣ ጋምቤላ፣ ሚዛን አማን እና ባኮ ከተሞች ቅርንጫፎች እየተከፈቱ ሲሆን...