News and Press

የፀደይ ባንኩ አትሌት ዳዊት ቢተው በ1500 ሜትር ውድድር የፍፃሜ ውድድሩን በ1ኛነት አጠናቀቀ።

የኢትዮጵያ ወጣቶች አትሌቲክስ ሻምፒዮና በሲዳማ ክልላዊ መንግስት ከሰኔ 25/2016 እስከ ሰኔ 29/2016 ዓ.ም በሀዋሳ ከተማ እየተካሄደ ይገኛል። የፀደይ ባንክ አትሌቲክስ ክለብም በውድድሩ በተወሰኑ አትሌቶች አማካኝነት እየተወዳደረ ይገኛል። በዚህ ውድድር የፀደይ ባንኩ አትሌት ዳዊት ቢተው በ1500 ሜትር 1ኛ በመሆን የወርቅ ሜዳልያ አስገኝቷል። በውድድሩ በበላይነት ያጠናቀቀው አትሌት ዳዊት የክለቡ ባለቤት የሆነው ፀደይ ባንክ በሀዋሳ ኢንተርናሽናል ስታዲየም በተደጋጋሚ እንዲተዋዎቅ ማስቻሉን የክለቡ ሥራ አስኪያጅ ደሳለው እንዳለው ያደረሰን መረጃ ያመላክታል። በሌላ ዜና የፀደይ ባንክ አትሌት መቅደስ ሽመልስ የመቻል (የመከላከያ) ስፖርት አዲስ አበባ ከተማ ላይ ከሰሞኑ ባዘጋጀው የ10 ኪሎ...

የፀደይ ባንክ አትሌት መቅደስ ሽመልስ በ10 ኪሎ ሜትር የሩጫ ውድድር በአንደኛነት አሸነፈች።

የፀደይ ባንክ አትሌት መቅደስ ሽመልስ በ10 ኪሎ ሜትር የሩጫ ውድድር በአንደኛነት አሸነፈች። የፀደይ ባንክ አትሌት መቅደስ ሽመልስ የመቻል (የመከላከያ) ስፖርት አዲስ አበባ ከተማ ላይ ዛሬ ባዘጋጀው የ10 ኪሎ ሜትር የአስፓልት ላይ ውድድር ነው በአንደኛነት ያጠናቀቀችው። በውድድሩ መብራት ግደይ እና ወርቅውኃ ጌታቸው ሁለተኛ እና ሦስተኛ ደረጃ በመያዝ አጠናቅቀዋል። "መቻል ለኢትዮጵያ" የጎዳና ላይ ሩጫ፣ መቻል ባለፉት 80 ዓመታት ለኢትዮጵያ ያበረከተውን አስተዋጽዖ ለማስታዎስ የተዘጋጀ ነው። ፀደይ ባንክ ከ2004 ዓ.ም ጀምሮ የራሱን አትሌቲክስ ክለብ በመመስረትና በጀት በመመደብ በርካታ ወጣት አትሌቶች ህልማቸውን እውን እንዲያደርጉና ሀገርን በዓለም መድረኮች እንዲያስጠሩ እያደረገ...

ይህን ያውቁ ኖሯል !

የኤ ቲ ኤም አገልግሎት በበረዷማው አሕጉር ውስጥ መኖሩን ያውቃሉ! ለመኖር እጅግ አስቸጋሪ በሆነው በበረዷማው አንታርክቲካ አሕጉር ውስጥ ሁለት የኤቲኤም ማሽኖች ይገኛሉ፡፡ የማሽኖቹ ባለቤት አሜሪካን ሀገር ሰን ፍራንሲስኮ የሚገኘው Wells Fargo የተባለ ባንክ ነው፡፡ አንታርክቲካ ውስጥ እንዲቀመጡና አገልግሎት እንዲሰጡ የተደረጉት ደግሞ እ.አ.አ ከ1998 ጀምሮ ነው፡፡ ለሰው ልጆች ለመኖር እጅግ ፈታኝ በሆነው አሕጉር ውስጥ ላለፉት 25 ዓመታት አገልግሎት በመስጠት ላይ የሚገኙት ሁለቱ የኤቲኤም ማሽኖች የተገጠሙት ማክ ሙርዶ (Mc Murdo) በተባለ የሳይንስ ጣቢያ አካባቢ ነው፡፡ ማሽኖቹ አገልግሎት እየሰጡ የሚገኙት ደግሞ በአሜሪካን ዶላር እንደሆነ የኢንዲያን ታይምስ...

በሞባይል ባንኪንግ ከሚፈጸሙ ማጭበርበሮች ይጠንቀቁ!

የሳይበር ምህዳር ይዟቸው ከመጣቸው መልካም አጋጣሚዎች መካከል በየዕለቱ ለምናደርጋቸው ግብይቶች ክፍያ ለመፈጸም ጥሬ ገንዘብ ከመጠቀም ይልቅ በዲጂታል የክፍያ ስርዓት መፈጸም ማስቻሉ ነው፡፡ በሞባይል የባንኪንግ አገልግሎት መጠቀም በጣም ምቹ፣ ቀላል፣ እና አዋጭ ነው፡፡ ይሁን እንጂ ዲጂታል የክፍያ አማራጮች ቀላልና ለአጠቃቀም ምቹ የመሆናቸውን ያህል በጥንቃቄ መጠቀም ካልቻልን ለአጭበርባሪዎች የመጋለጥ እድላችንን ይጨምራል፡፡ ይህ እውነታ ለባንክ መተግበሪያዎች ሲሆን ደግሞ በተለያዩ ምክንያቶች የሚከሰቱ የደኅንነት ስጋቶችን ክፍተኛ ያደርገዋል። አጭበርባሪዎች ሊጠቀሙባቸው የሚችሉ የማብጭበርበሪያ መንገዶች ምን ምን ሊሆኑ ይችላሉ? ከባንክ ነው የደወልንልዎት የሚሉ የማጭበርበርያ ጽሑፎች እና የስልክ ጥሪዎች፣ አካላዊ የስልክ ስርቆት እና ምንተፋ፣ የፋይናንስ...

ከደንበኞቻችን አንደበት

“ፀደይ ባንክ እንደቤቴ የማየው ቀኝ እጄ ነው፤ ስኬታማ መሆን የቻልሁት ባገኘሁት ብድር በመሆኑ ደስተኛ ነኝ፡፡” “ወ.ሮ ቤዛዊት ተስፋዬ  እባላለሁ የመብራት እና ፊኒሺንግ እቃዎች መሸጫ ሱቅ ባለቤት ነኝ፡፡ ላለፉት ስድስት ዓመታት ከፀደይ ባንክ ጋር እየሠራሁ እገኛለሁ፡፡ ከባንኩ ከሁለት ጊዜ በላይ ብድር በመውሰድ የመኖሪያ ቤት መሥራት እና በንግዱም ዘርፍ ውጤታማ መሆን ችያለሁ፡፡ ፀደይ ባንክ እንደቤቴ የማየው ቀኝ እጄ ነው፤ ስኬታማ መሆን የቻልሁት ባገኘሁት ብድር በመሆኑ ደስተኛ ነኝ፡፡”

Tsedey Bank S.C and Lemi National Cement PLC agrees to partner up

Tsedey Bank and Lemi National Cement PLC decided to partner up following extensive talks between senior executives. Following the agreement, a delegation from Tsedey Bank's executive management team visited Lemi National Cement PLC. Tsedey Bank is a prominent Ethiopian private commercial bank with a paid up capital of Birr 9.833 billion. The bank's financial strength is further reflected in its total assets and capital, which stand at Birr 56.6 billion and Birr 12.8 billion, respectively. It has over 14,000,000 total customers...

ግብይትዎ በአጭበርባሪዎች እንዳይስተጓጎል ይጠንቀቁ፤ በጥንቃቄ ይከውኑ!

በተለይም ሐሰተኛ የብር ኖቶችን ከሚያዘዋውሩ አጭበርባሪዎች ይጠንቀቁ! በ 200፣ 100 እና 50 ብር ላይ የሚገኙ የደኅንነት መጠበቂያ ምልክቶች እና ምስሎችን በአግባቡ ያስተውሉ፡፡ በተጨማሪም ግብይትዎን ደኅንነቱ አስተማማኝ በሆነው የፀደይ ሞባይል ባንኪንግ የክፍያ አማራጮች ያከናውኑ። Join us on our digital media platforms: Website (https://tsedeybank-sc.com/)Telegram (https://t.me/tsedeybanksc)Twitter (https://twitter.com/TsedeyBankSC)LinkedIn (https://www.linkedin.com/company/tsedey-bank-s-c/)Facebook (https://www.facebook.com/TsedeyBankSC)TikTok (http://www.tiktok.com/@tsedeybanksc)Youtube (https://youtube.com/@TsedeyBank)

ፀደይ ባንክ ቅርንጫፎቹን በሁሉም የሀገሪቱ ክፍሎች እያስፋፋ ነው፡፡

ፀደይ ባንክ የባንክ አገልግሎት መስጠት ከጀመረ ወዲህ ተጨማሪ 142 ቅርንጫፎችን መክፈቱን የባንኩ የዲጂታልና ብራንች ባንኪንግ ም/ፕሬዚዳንት አቶ ቴዎድሮስ ታደሰ ተናግረዋል፡፡ ይህ ዘገባ እስከተጠናቀረበት ጊዜ ድረስም የባንኩን ቅርንጫፎች ብዛት 608 ማድረስ ተችሏል፡፡ በደቡብ የሀገሪቱ ክፍል አርባ ምንጭ፣ ወላይታ ሶዶ፣ ዲላ፣ ሆሳዕና፣ ይርጋ ጨፌ፣ ሻሸመኔ እና ሀዋሳ ከተሞች ላይ ቅርንጫፎች ተከፍተው አገልግሎት እየሰጡ መሆኑን ያስረዱት አቶ ቴዎድሮስ በምስራቁ የሀገሪቱ ክፍል ደግሞ ድሬዳዋ፣ ሎጊያና አሳይታ ከተሞች ቅርንጫፎች መከፈታቸውን ገልጸዋል፡፡ በደቡብ ምዕራቡ የሀገሪቱ ክፍል ደግሞ ጅማ፣ ጋምቤላ፣ ሚዛን አማን እና ባኮ ከተሞች ቅርንጫፎች እየተከፈቱ ሲሆን...

የፀደይ ባንኩ አትሌት በዓለም ሻምፒዮና!

የፀደይ ባንኩ አትሌት ይስማው ድሉ በሰርቢያ ቤልግሬድ እየተካሄደ በሚገኘው 45ኛው የዓለም ሀገር አቋራጭ ሻምፒዮና 4ኛ በመሆን የዲፕሎማ ደረጃ አግኝቷል። አትሌቱ ኢትዮጵያ በቡድን የብር ሜዳልያ እንድታገኝም ከፍተኛውን አስተዋፅዖ አበርክቷል። ዛሬ በ8 ኪ.ሜትር ወጣት ወንዶች በተካሄደው ውድድር ኢትዮጵያ በቡድን 2ኛ በመሆን የብር ሜዳልያ እንድታገኝ የፀደይ ባንኩ አትሌት ይስማው ከሌሎች ኢትዮጵያውያን የቡድን አጋሮቹ ጋር ብርቱ ጥረት አድርጓል። የፀደይ ባንክ አትሌቲክስ ክለብ አትሌቱ ይስማው ድሉ ጥር 05/2016 ዓ.ም በተካሄደው 41ኛው የጃንሜዳ ኢንተርናሽናል አትሌቲክስ አገር አቋራጭ ውድድር ነበር በሰርቪያ ቤልግሬድ ለሚካሄደው የዓለም አትሌቲክስ አገር አቋራጭ ውድድር ኢትዮጵያን...

Tsedey Bank invests heavily in women’s empowerment!

Tsedey Bank supports women's empowerment through strategic investment.Tsedey Bank is demonstrably committed to fostering women's empowerment through targeted financial initiatives. Recognizing the crucial role women play in economic development, the bank has strategically allocated a significant portion of its loan portfolio, reaching nearly 50% disbursement to women-owned businesses and enterprises. This commitment reflects Tsedey Bank's deep understanding of the positive societal and economic impact achieved by empowering women.Empowering women is a strategic investment that equips them with the resources...

Feedback

    Copyright © 2023 Tsedey Bank S.C. | All Rights Reserved

    Call Center / ነጻ የጥሪ ማዕከል፡ 8220