News and Press

የፀደይ ባንክ አትሌቶች በሳፋሪኮም ኢትዮጵያ 5 ኪ.ሜ ውድድር አሸነፉ።

የፀደይ ባንክ አትሌቲክስ ክለብ አትሌቶች ዛሬ መጋቢት 07/2017 ዓ.ም በተካሄደው የሳፋሪኮም ኢትዮጵያ ቅድሚያ ለሴቶች 5 ኪ.ሜ ውድድር አሸናፊ ሆነዋል። ውድድሩ በየዓመቱ የሚዘጋጅ፣ በርካታ ልምድ ያላቸው እና ጠንካራ ሴት አትሌቶች የሚሳተፉበት ነው። በዚህ የ 5 ኪ.ሜ የጎዳና ላይ ውድድር የፀደይ ባንክ አትሌቲክስ ክለብ አትሌት ብርነሽ ደሴ 1ኛ፣ አትሌት መቅደስ ሽመልስ ደግሞ 3ኛ በመውጣት አሸንፈዋል። በውድድሩ 2ኛ የወጣችው የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ አትሌት አበዙ ከበደ ናት። በዚህ ውድድር ባለፈው ዓመት አትሌት ብርነሽ ደሴ 2ኛ፣ አትሌት መቅደስ ሽመልስ ደግሞ 3ኛ በመውጣት ማጠናቀቃቸው ይታወሳል። በርካታ ማኅበራዊ ኃላፊነቶችን እየተወጣ የሚገኘው...

Unite.et ላይ በመመዝገብ የፀደይ ባንክ ደንበኛ ይሁኑ!

Unite.et ላይ በመመዝገብ የፀደይ ባንክ ደንበኛ ይሁኑ! በቀላሉ በመመዝገብ የፀደይ ባንክ ደንበኛ ለመሆን ቀጥሎ ያሉትን ሂደቶች ይከተሉ! የ Unite.et መተግበሪያን ከአፕ ስቶር ወይም ከፕሌይ ስቶር ያውርዱ፣ ፀደይ ባንክ የሚለውን ይምረጡ፣ የምዝገባ ቅደም ተከተሉን በመከተል ይመዝገቡ! ከዚያም የዲያስፖራ አገልግሎቶቻችን ተጠቃሚ ይሁኑ! ስለመረጡን፣ አብረውን ስለሚሠሩ ከልብ እናመሠግንዎታለን!

የሁሉም ባንክ!Bank for all!

ፀደይ ባንክ እና ጤና ሚኒስቴር በጋራ ለመሥራት ተፈራረሙ፡፡

ፀደይ ባንክ የዲጂታል ጤና ክፍያ የሙከራ ትግበራ ላይ በጋራ ለመሥራት ከጤና ሚኒስቴር ጋር የመግባቢያ ሰነድ ተፈራርሟል፡፡ የፊርማ ሥነ-ሥርዐቱ ዛሬ የካቲት 26/2017 ዓ.ም በጤና ሚኒስቴር ግቢ ውስጥ ነው የተከናወነው፡፡ ስምምነቱን የፀደይ ባንክ ፕሬዝዳንት አቶ መኮንን የለውምወሰን እና የጤና ሚኒስትሯ ዶክተር መቅደስ ዳባ ናቸው የተፈራረሙት፡፡ በርካታ የዲጂታል የባንክ አገልግሎቶችን እየሰጠ የሚገኘው ፀደይ ባንክ የዲጂታል ጤና ክፍያዎችን የሙከራ ትግበራ ለማስጀመር በጤና ሚኒስቴር ከተመረጡ የፋይናንስ ተቋማት መካከል አንዱ ሆኗል፡፡ በስምምነቱ መሠረትም ባንኩ የዲጂታል ጤና ክፍያዎችን የሙከራ ትግበራ የሚያስጀምር ይሆናል፡፡ ፀደይ ባንክ በዲጂታል የባንክ አገልግሎት ዘርፍ የሞባይል፣ የኢንተርኔት፣...

ባንኩ የተሻለ አፈጻጸም ላስመዝገቡ ቅርንጫፎች እና ዲስትሪክቶች እውቅና ሰጠ፡፡

ፀደይ ባንክ በ2024/2025 በጀት ዓመት የመጀመሪያ ስድስት ወራት የተሻለ አፈጻጸም ላስመዝገቡ ቅርንጫፎች እና ዲስትሪክቶች እውቅና ሰጥቷል፡፡ ፀደይ ባንክ የ2024/2025 በጀት ዓመት የመጀመሪያ አጋማሽ አፈጻጸሙን በተመለከተ ከሰሞኑ ተወያይቷል፡፡ በዚህም የተለያዩ መመዘኛዎችን መሠረት በማድረግ የሁሉም ዲትሪክቶች እና ቅርንጫፎች አፈጻጸም ላይ ውይይት በማካሄድ በቀጣይ በትኩረት መፈጸም ያለባቸው ዐበይት ነጥቦችን አስቀምጧል፡፡ ይህን ተከትሎም የተሻለ አፈጻጸም ላስመዘገቡ ዲስትሪክቶች እና ቅርንጫፎች እውቅና እና ሽልማት ሰጥቷል፡፡ ደሴ፣ ወልድያ እና ሰቆጣ ዲስትሪክቶች የዋንጫ ሽልማት ተበርክቶላቸዋል፡፡ በተጨማሪም ከደሴ ዲስትሪክት፡- ዋርካ እና ፒያሳ፤ ከአዲስ አበባ ዲስትሪክት፡-አራት ኪሎ፤ ከፍኖተ ሠላም ዲስትሪክት፡- ብራቃት፤ ከደብረ ብርሃን...

የፀደይ ባንክ አትሌት ኢትዮጵያን በአፍሪካ ውድድር መወከል የሚያስችላትን ውጤት አስመዘገበች።

የፀደይ ባንክ አትሌት ኢትዮጵያን በአፍሪካ ውድድር መወከል የሚያስችላትን ውጤት አስመዘገበች። በ42ኛው የጃንሜዳ ኢንተርናሽናል አትሌቲክስ አገር አቋራጭ ውድድር የፀደይ ባንክ አትሌት መቅደስ ሽመልስ በ10 ኪ.ሜ አዋቂ ሴቶች 4ኛ በመሆን አጠናቅቃለች። ዛሬ ጥር 25/2017 ዓ.ም በተካሄደው ውድድር ያስመዘገበችው ውጤትም ኢትዮጵያን በአሕጉር አቀፍ ውድድር መወከል እንደሚያስችላት የክለቡ ሥራ አስኪያጅ ደሳለው እንዳለው ያደረሰን መረጃ ያመላክታል። ...

የኤቲኤም ማሽን ሲጠቀሙ ደኅንነትዎ መጠበቁን ያረጋግጡ!

የኤቲኤም ማሽን ሲጠቀሙ ደኅንነትዎ መጠበቁን ያረጋግጡ! የኤቲኤም ማሽን ሲጠቀሙ ደኅንነትዎ መጠበቁን ያረጋግጡ! የምስጢር ቁጥርዎን ሲያስገቡ ሌሎች እንዳይመለከቱ ይሸፍኑ፡፡ የምስጢር ቁጥርዎን ለሌላ ሰው አያሳዩ (አሳልፈው አይስጡ)፡፡ ከማያውቁት ሰው የሚመጣን እገዛ አይቀበሉ፡፡ የባንክ ሒሳብ መረጃዎን በየጊዜው ይከታተሉ፡፡ Stay Safe at the ATMTo enhance your security while using ATMs: Shield the keypad with your hand while entering your (PIN) to prevent unauthorized viewing. Refuse offers of assistance from strangers, as they may have ill intentions. Regularly review your account transactions for any suspicious or unauthorized activity. የሁሉም ባንክ!Bank for all!

ርእሰ መሥተዳድር አረጋ ከበደ የፀደይ ባንክን የዋና መሥሪያ ቤት ሕንጻ የግንባታ ሂደት ጎበኙ፡፡

የአማራ ክልል ርእሰ መሥተዳድር አረጋ ከበደ የፀደይ ባንክን የዋና መሥሪያ ቤት ሕንጻ የግንባታ ሂደት ጎብኝተዋል፡፡ ፀደይ ባንክ ዋና መሥሪያ ቤቱን በአዲስ አበባ-ሰንጋ ተራ ላይ እያስገነባ ይገኛል፡፡ የባንኩ ባለ 37 ወለል ሕንጻ የግንባታ ሂደትንም ርእሰ መሥተዳድር አረጋ ከበደ ዛሬ ጥር 17/2017 ዓ.ም ጎብኝተዋል፡፡ ከጉብኝታቸው በኋላም ከባንኩ የማኔጅመንት አባላት ጋር ተወያይተዋል። የፀደይ ባንክ ዋና መሥሪያ ቤት አጠቃላይ የቦታ ስፋት 4,024 ሜትር ስኩዌር ሲሆን ግንባታው ያረፈበት ቦታ ደግሞ 3,220 ሜትር ስኩዌር ይሸፍናል፡፡ የፀደይ ባንክ ዋና መሥሪያ ቤት ግንባታ ከ4 ነጥብ 7 ቢሊዮን ብር በላይ እንደሚያስፈልገው ይጠበቃል፡፡ ፀደይ ባንክ በግንባታ...

አዲስ ዜና አለን!፡

ለክቡራን ደንበኞቻችን! የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ በሰጠው መመሪያ መሰረት ከዛሬ ረቡዕ ታኅሣሥ 23 ቀን 2017 ዓ.ም (January 1, 2025) ጀምሮ በአዲስ አበባ ውስጥ በሚገኙ ሁሉም የባንካችን ቅርንጫፎች አዲስ የባንክ ሒሳብ ለመክፈት የምትመጡ ደንበኞች የፋይዳ ዲጂታል መታወቂያ መያዝ ያለባችሁ መሆኑን በአክብሮት እናስታውቃለን፡፡ የሁሉም ባንክ!Bank for all!

የጠቅላላ ጉባኤ ጥሪ ማስታዎቂያ

የፀደይ ባንክ አ.ማ የባለአክሲዮኖች 5ኛ መደበኛ ጠቅላላ ጉባኤ እና 3ኛ አስቸኳይ ጠቅላላ ጉባኤ  የጉባኤ ጥሪ በኢትዮጵያ ንግድ ህግ ቁጥር 1243/2013 አንቀጽ 366፤ 367፤ 370፤371 እና 372 እንዲሁም በአክሲዮን ማህበሩ መመስረቻ ጽሁፍ አንቀፅ 14 (3) መሠረት የፀደይ ባንክ አ.ማ የባለአክሲዮኖች 5ኛ መደበኛ ጠቅላላ ጉባኤ እና 3ኛ አስቸኳይ ጠቅላላ ጉባኤ ሰኞ ታኅሣስ 21 ቀን 2017 ዓ.ም ከጠዋቱ 3፡00 ሰዓት ጀምሮ በሂልተን ሆቴል ይካሄዳል፡፡ በመሆኑም የተከበራችሁ የማኅበሩ ባለአክሲዮኖች በዕለቱ በጉባኤው እንድትገኙልን የማኅበሩ የዳይሬክተሮች ቦርድ ጥሪውን ያስተላልፍል። ማኅበሩን የሚመለከቱ ዋና ዋና መረጃዎች፤ የአክሲዮን ማኅበሩ ዋና መሥሪያ ቤት...

የጨረታ ማስታዎቂያ

ፀደይ ባንክ (አ.ማ) ለአቶ ጌታቸው አባት ለሰጠው ብድር በዋስትና የያዛቸውን በሰንጠረዡ የተዘረዘሩ መኖሪያ ቤቶችን በአዋጅ ቁጥር 97/90 በተሸሻለው አዋጅ ቁጥር 216/92 በተሰጠው ስልጣን መሰረት በግልጽ ጨረታ አወዳድሮ ለመሸጥ ይፈልጋል፡፡ በመሆኑም ተጫራጮች ለጨረታ ከመቅረባቸው በፊት የሚከተሉትን ደንቦች መገንዘብ ይኖርባቸዋል፡፡ ተጫራጮች የቤቱን የጨረታ መነሻ ዋጋ ¼ (በጥሬ ገንዘብ ወይም ሲ.ፒ.ኦ በፀደይ ባንክ ስም (አ.ማ) በማሰራት ለጨረታ ማስከበሪያ በማስያዝ በጨረታው መሳተፍ ይችላሉ፡፡ በጨረታው የሚሳተፈው በሕግ ሰውነት ያገኘ ሰው ከሆነ የድርጅቱ መመሥረቻ ጽሑፍ ወይም መተዳደሪያ ደንብ፣ ሕጋዊ ሰውነት ያገኘበት የምዝገባ የምስክር ወረቀት እንዲሁም ሕጋዊ ውክልና ማቅረብ...