News and Press

ፀደይ ባንክ ከ12ኛ ክፍል ከፍተኛ ውጤት ላስመዘገቡ ተማሪዎች የማበረታች ሽልማት ሰጠ፡፡

ፀደይ ባንክ በ2015 ዓ.ም የ12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና ወስደው ከፍተኛ ውጤት ላመጡ ተማሪዎች 6 መቶ ሺህ ብር የማበረታቻ ሽልማት ሰጥቷል፡፡ ሽልማቱን የሰጠው ታኅሳስ 14/2016 ዓ.ም ነው፡፡ከዚህ ባሻገር ባንኩ ከ8ኛ ወደ 9ኛ ክፍል በከፍተኛ ውጤት ላለፉና ድጋፍ ለሚሹ ተማሪዎች የዩኒቨርሲቲ ትምሕርታቸውን እስኪያጠናቅቁ ድረስ ድጋፍ በማድረግ በርካታ ጎበዝ ተማሪዎች ሕልማቸውን እውን እዲያደርጉ እየሠራ መሆኑም ይታዎቃል፡፡ ይህ መርሐ-ግብር ‹‹ብቁ›› የሚል ስያሜ ያለውና ከ2005 ዓ.ም ጀምሮ እየተተገበረ የሚገኝ ነው፡፡ለትምሕርት ዘርፉ ድጋፍ በማድረግ ደማቅ አሻራ ያለው ፀደይ ባንክ የትምህርት ቤት ግንባታ ብዙም ባልተስፋፋበት ዋግ ኽምራ ብሔረሰብ...

ፀደይ ባንክ የሞባይል እና ኢንተርኔት ባንኪንግ አገልግሎቶችን በይፋ አስጀመረ፡፡

ባንኩ የሞባይል እና ኢንተርኔት ባንኪንግ አገልግሎት ማስጀመሩን አስመልክቶ ዛሬ ታኅሳስ 10/2016 ዓ.ም በሸራተን አዲስ ሆቴል ለመገናኛ ብዙኃን መግለጫ ሰጥቷል። የፀደይ ባንክ ፕሬዝዳንት አቶ መኮንን የለውምወሰን ባንኩን በቴክኖሎጂ ለማዘመን እየተሠራ  መሆኑን ገልጸዋል፡፡ ዛሬ በይፋ ሥራ የጀመሩት የሞባይል እና ኢንተርኔት ባንኪንግ አገልግሎቶችም የዚህ አካል መሆናቸውን አስረድተዋል፡፡ የሞባይል ባንኪንግ አገልግሎቱ ዘመናዊነትን የተላበሰ ስለመሆኑ የገለጹት ፕሬዝዳንቱ ደንበኞች ራሳቸው መመዝገብ የሚችሉበት፣ ከምስጢር ቁጥር በተጨማሪ በአሻራ እና በባዮሜትሪክስ አገልግሎት መሥጠት የሚያስችል መሆኑንም አብራርተዋል፡፡ በቀጣይም ባንኩን ተወዳዳሪ የሚያደርጉ እና የደንበኞችን ፍላጎት የሚያሟሉ አዳዲስ ቴክኖሎጂዎችን እንደሚያስተዋውቅም ነው የገለጹት፡፡ ደንበኞች በማንኛውም ዓይነት...

ከውጭ ሀገራት የሚላክልዎትን ገንዘብ በፀደይ ባንክ በኩል ይቀበሉ!

💵ከውጭ ሀገራት የሚላክልዎትን ገንዘብ በፀደይ ባንክ በኩል ይቀበሉ! 💶ከውጭ ሀገራት በዓለም አቀፍ የገንዘብ አስተላላፊ ድርጅቶች አማካኝነት የሚላክልዎትን ገንዘብ  በፀደይ ባንክ ይቀበሉ፤ ይመንዝሩ! 🌍ከየትኛውም የዓለማችን ክፍል ገንዘብ ለወዳጅ ዘመድዎ መላክ ሲፈልጉ ፈጣን፣ ቀላል እና አስተማማኝ የሆነውን የፀደይ ባንክ ስዊፍት ኮድ (Swift code): TSDYETAA  ይጠቀሙ፡፡ ፀደይባንክ! የሁሉምባንክ! TsedeyBank! Bankforall Tsedey Bank S.C

የፀደይ ባንክ አ.ማ የባለአክሲዮኖች 3ኛ መደበኛ ጠቅላላ ጉባኤ ጥሪ

ለተከበራችሁ የፀደይ ባንክ አ.ማ ባለአክሲዮኖች፤ የፀደይ ባንክ አማ የባለአክሲዮኖች 3ኛው መደበኛ ጠቅላላ ጉባዔ በኢትዮጵያ ንግድ ህግ ቁጥር 1243/2013 አንቀጽ 366፤ 367፤ 370፤371 እና 372 መሠረት ቅዳሜ ታህሳስ 20 ቀን 2016 ዓ.ም ከጠዋቱ 2፡30 ሰዓት ጀምሮ ሀይሌ ግራንድሆቴል ይካሄዳል፡፡ስለሆነም የባንኩ ባለአክሲዮኖች በአካል ወይም በህጋዊ ወኪሎቻችሁ አማካኝነት በተጠቀሰው ቀን: ሰዓት እና ቦታ እንድትገኙ የዳይሬክተሮች ቦርድ ጥሪውን በአክብሮት ያቀርባል፡፡ ስለ ባንኩ መግለጫ፡- የባንኩ የተፈረመ ካፒታል፡ ብር 9837889000.00 የባንኩ የተከፈለ ካፒታል፡ ብር 9833346177.00 የባንኩ ዋና የንግድ ምዝገባ ቁጥር ፡  MT/AA/3/0052707/2014 የባንኩ የሥራ ፈቃድ ቁጥር: LBB/TM/026/2022       የባንኩ አድራሻ፡አዲስ አበባ ከተማ፣ቂርቆስ ክፍለከተማ፣ ወረዳ07፣ለገሃርመብራት...

ፀደይ ባንክ በድርቅ ለተጎዱ ወገኖች 50 ሚሊዮን ብር ድጋፍ አደረገ።

ድጋፉ ለተጎጂዎች በአመልድ ኢትዮጵያ በኩል የሚደርስ ይሆናል። በዚህም መሠረት የፀደይ ባንክ ፕሬዚደንት አቶ መኮንን የለውምወሰን የ 50 ሚሊዮን ብር ድጋፉን ለአመልድ ኢትዮጵያ ዋና ዳይሬክተር ዶክተር ዓለማየሁ ዋሴ ዛሬ ኅዳር 22/03/2016 ዓ.ም በዋናው መሥሪያ ቤት በተካሄደ መርሐ-ግብር አስረክበዋል። የባንኩ ፕሬዚዳንት አቶ መኮንን የለውምወሰን ለመገናኛ ብዙኃን በሰጡት መግለጫ የሰዎች ሞት ጭምር ያስከተለውን የድርቅ እና የረሃብ ችግር ለመቋቋም የሚደረገውን ጥረት ለማገዝ አስቦ ድጋፍ መሰጠቱን ተናግረዋል። ባለፈው በጀት ዓመት ብቻ እስከ 200 ሚሊዮን ብር ለተለያዩ ማኅበራዊ ጉዳዮች ድጋፍ ማድረጉንም አስታውሰዋል። የአመልድ ኢትዮጵያ ዋና ዳይሬክተር ዶ.ር ዓለማየሁ ዋሴ...

አነስተኛ ብድርና ቁጠባ ተቋማት ለፋይናንስ አቅርቦት ተደራሽነትና ለሥራ ዕድል ፈጠራ የላቀ ሚናቸውን ሊወጡ እንደሚገባ ተመላከተ፡፡

የኢትዮጵያ አነስተኛ ብድርና ቁጠባ ተቋማት ማኅበር 25ኛ ዓመት የምስረታ በዓል በፓናል ውይይት፣ በአውደ ርዕይ እና በልዩ ልዩ ዝግጂቶች እየተከበረ ነው፡፡ የፀደይ ባንክ ፕሬዚዳንት እና የማኅበሩ የቦርድ ሰብሳቢ አቶ መኮንን የለውምወሰን አነስተኛ የፋይናንስ ተቋማት ለኢኮኖሚ እና ለማኅበራዊ ልማት ያላቸውን አስተዋጽኦ በሚመለከት ሀሳብ አቅርበዋል፡፡ ለፋይናንስ አቅርቦት ተደራሽነትና ለዜጎች የሥራ ዕድል ፈጠራ አነስተኛ ብድርና ቁጠባ ተቋማት ሚናቸውን አጠናክረው ሊቀጥሉ እንደሚገባም በመድረኩ ተነስቷል፡፡ የኢትዮጵያ አነስተኛ ብድርና ቁጠባ ተቋማት ማኅበር 25ኛ ዓመት የምስረታ በዓል "ማይክሮ ፋይናንስ በዲጂታል ዘመን የፋይናንስ አካታችነት ለሥራ ፈጠራና ለሴቶች የኢኮኖሚ ተጠቃሚነት” በሚል መሪ ሃሳብ...

የፀደይ ባንክ የዳይሬክተሮች ቦርድ አባላት ምልመላ እና አስመራጭ ኮሚቴ ማስታወቂያ

ለፀደይ ባንክ አ.ማ የዳይሬክተሮች ቦርድ አባልነት ዕጩ ሆነዉ የተመረጡ 24 (ሃያ አራት) ዕጩ የዳይሬክተሮች ቦርድ አባላት እና 12 (አስራ ሁለት) ተጠባባቂዎች የፀደይ ባንክ አ.ማ ባለአክስዮኖች ህዳር 22 ቀን 2015 ዓ.ም ባካሄዱት 1ኛ መደበኛ ጠቅላላ ጉባዔ በ2016 ዓ.ም በሚካሄደዉ 3ኛ መደበኛ ጠቅላላ ጉባዔ በሚደረገዉ የዳይሬክተሮች ቦርድ አባላት ምርጫ ዕጩ የዳይሬክተሮች ቦርድ አባላትን መልምሎ የሚያቀርብ የዳይሬክተሮች ቦርድ አባላት ምልመላ እና አስመራጭ ኮሚቴ መሰየሙ ይታወሳል፡፡ በዚህም መሰረት የምልመላ እና አስመራጭ ኮሚቴዉ በኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ መመርያ ቁጥር SBB/71/2019 እና SBB/79/2021 አግባብነት ባላዉ የባንኩ መመስረቻ ደንብ...

የፀደይ ባንክ የዳይሬክተሮች ቦርድ አባላት ምልመላ እና አስመራጭ ኮሚቴ ማስታወቂያ

ለፀደይ ባንክ አ.ማ የዳይሬክተሮች ቦርድ አባልነት ዕጩ ሆነዉ የተመረጡ 24 (ሃያ አራት) ዕጩ የዳይሬክተሮች ቦርድ አባላት እና 12 (አስራ ሁለት) ተጠባባቂዎች አዲስ ዘመን እሑድ ኅዳር 16 ቀን 2016 ዓ.ም የፀደይ ባንክ አ.ማ ባለአክሲዮኖች ህዳር 22 ቀን 2015 ዓ.ም ባካሄዱት 1ኛ መደበኛ ጠቅላላ ጉባዔ በ2016 ዓ.ም በሚካሄደዉ 3ኛ መደበኛ ጠቅላላ ጉባዔ በሚደረገዉ የዳይሬክተሮች ቦርድ አባላት ምርጫ ዕጩ የዳይሬክተሮች ቦርድ አባላትን መልምሎ የሚያቀርብ የዳይሬክተሮች ቦርድ አባላት ምልመላ እና አስመራጭ ኮሚቴ መሰየሙ ይታወሳል፡፡ በዚህም መሠረት የምልመላ እና አስመራጭ ኮሚቴዉ በኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ መመርያ ቁጥር SBB/71/2019 እና...

አዲስ ነገር አለ! በቅርብ ቀን በእጅዎ!

በቅርብ ቀን አዲስ ነገር... በእጅዎ! ከፀደይ ባንክ! ለሚሊዮኖች ኑሮ መሻሻል ከሚተጋው ከፀደይ ባንክ ጋር ይሥሩ! ለሕልምዎ እውን መሆን! ለአስተማማኝ የፋይናንስ አቅርቦት! ጠቀም ላለ ወለድ! ለፈጣንና አስደሳች አገልግሎት! ከግዙፉ ፀደይ ባንክ ጋር ይሥሩ! • የፀደይ ባንክ ትክክለኛ የዲጂታል ሚዲያ ገፆችን በእነዚህ ሊንኮች ይቀላቀሉ።•Website: https://tsedeybank-sc.com/•Telegram:https://t.me/tsedeybanksc•Twitter: https://twitter.com/TsedeyBankSC•LinkedIn: https://www.linkedin.com/company/tsedey-bank-s-c/•Facebook: https://www.facebook.com/TsedeyBankSC•TikTok: www.tiktok.com/@tsedeybanksc•Youtube:https://youtube.com/@TsedeyBank ፀደይባንክ! የሁሉምባንክ! TsedeyBank! Bankforall

Privacy Policy

Welcome to Tsedey Bank. At Tsedey Bank, we prioritize the protection of your privacy and personal data. This Privacy Policy outlines our policies and procedures regarding the collection, usage, and disclosure of your information when you use our mobile application. Interpretation and Definitions1.1. InterpretationThe capitalized words have specific meanings, as defined under certain conditions. These definitions remain consistent whether they appear in singular or plural form.1.2. DefinitionsFor the purpose of this Privacy Policy:Account: Refers to a unique account created for you...

Feedback

    Copyright © 2023 Tsedey Bank S.C. | All Rights Reserved

    Call Center / ነጻ የጥሪ ማዕከል፡ 8220