ፀደይ ባንክ ከ12ኛ ክፍል ከፍተኛ ውጤት ላስመዘገቡ ተማሪዎች የማበረታች ሽልማት ሰጠ፡፡
ፀደይ ባንክ በ2015 ዓ.ም የ12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና ወስደው ከፍተኛ ውጤት ላመጡ ተማሪዎች 6 መቶ ሺህ ብር የማበረታቻ ሽልማት ሰጥቷል፡፡ ሽልማቱን የሰጠው ታኅሳስ 14/2016 ዓ.ም ነው፡፡ከዚህ ባሻገር ባንኩ ከ8ኛ ወደ 9ኛ ክፍል በከፍተኛ ውጤት ላለፉና ድጋፍ ለሚሹ ተማሪዎች የዩኒቨርሲቲ ትምሕርታቸውን እስኪያጠናቅቁ ድረስ ድጋፍ በማድረግ በርካታ ጎበዝ ተማሪዎች ሕልማቸውን እውን እዲያደርጉ እየሠራ መሆኑም ይታዎቃል፡፡ ይህ መርሐ-ግብር ‹‹ብቁ›› የሚል ስያሜ ያለውና ከ2005 ዓ.ም ጀምሮ እየተተገበረ የሚገኝ ነው፡፡ለትምሕርት ዘርፉ ድጋፍ በማድረግ ደማቅ አሻራ ያለው ፀደይ ባንክ የትምህርት ቤት ግንባታ ብዙም ባልተስፋፋበት ዋግ ኽምራ ብሔረሰብ...